• Call Us
  • +251..........

የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ክልላዊ መድረክ እየተካሄደ ነዉ

የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ክልላዊ መድረክ እየተካሄደ ነዉ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ክልላዊ መድረክ  ርዕሰ መስተዳደር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በወላይታ ሶዶ እየተካሄደ ይገኛል ።

'' የመሃሉ ዘመንን መረዳት 'በሚል ሃሳብ እየተካሄደ ባለው በዚሁ መድረክ፦ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጨላን ጨምሮ ሌሎች  ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ይገኙበታል ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ በዚህ ወቅት ፦ባለፉት ሰባት የለውጡ አመታት በክልሉ ብሎም በሀገሪቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን በቀጣይም በዘላቂነት ለማስቀጠል እንደሆነ አስታውቋል ።

መድረኩ በተለይ፦ የህዝብን አንድነት በማጠናከርና ያሉት ፈተናዎች ወደ ድል በመቀየር የሚፈለገውን ብልጽግና ለማረጋገጥ እንደሆነም ነዉ ርዕሰ መስተዳድሩ የገለፁት ።

የተመዘገቡት ስኬቶችን የበለጠ  ዉጤታማ ለማድረግ አመራሩ ይበልጥ እንዲዘጋጁ የሚያስችል መድረክ መሆኑን አቶ ጥላሁን ጥላሁን ከበደ አስረድተዋል ።

በመድረኩ "የመሐሉ ዘመን" በሚል ሃሳብ የተዘጋጀ   ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።